Tuesday 24 July 2012

በምታውቀው ልክ መኖር


                                 
በምታውቀው ልክ እንደመኖር ከባድ ነገር የለም። እስቲ አስቡት ከልጅነታችሁ ጀምሮ የተነገራችሁን ፣ የተረዳችሁትን እና የተቀበላችሁትን ። 
-ጊዜህን ባግባቡ ተጠቀም የተባላችሁበት ዘመን ዘመን የለውም።
-የምትናገረውን እጥፍ ያህል አዳምጥ ተባላችሁም ይሆናል( ይህን መርህ ተናጋሪውም አድማጩም ቢተገብሩት ምን እንደሚፈጠር ባይታወቅም።)
-ለነገ አትጨነቅ
-በራስህ ተማመን
-ሃሳቡን አንጅ ሰውየውን አትቃወም
-ሃጥያቱን እንጅ ሃጥያተኛዉን አትጥላ
-አታጭስ  አትቃም  አብዝተህ አት  ታምኝ ሁንጠንክረህ ስራ
በርትታህ ተማር
ኧረ ስንቱ   የሰው ልጅ የህይወት ትግል እንዲህ በማወቅ፣ በመቀበል እና በመርዳት ነገርግን በእውቀት ልክ መተግበር ባለመቻል የተሞላ ነው።

ሊያርመው፣ ሊያሻሽለው፣ ሊቀይረው የሚፈልገው ምንም ነገር የሌለው ሰው አይቸ አላውቅም። ካወቃቻሁ አደራ አንድትነግሩኝ። ምናልባት እሱ እያንዳንዱን ድርጊቱን በስሜት ፣ እንደተመቸው ወይም በወቅቱ እንደመሰለው ሳይሆን በሚያምንበት መርሁ የመራ መሆን አለበት።

ማድረግ ያለብንን እናውቃለን፤ ማድረግ ያለብንን ሁሉ ግን አናደርግም። የተሻለውን እና የተቀደሰውን መንገድ እንገነዘባለን፤ ያንኑ መንገድ መከተል ግን በቀላሉ አይሆንልም። በዚህም የተነሳ ህይወታችን ተወጥነው ባልተቋጩ እቅዶች፣ ተጀምረው ባልተፈጸሙ መንገዶች የተሞላ ነው። አንድ ቀን፣ ቃ አንድ ቀን ማድረግ የምንፈልገው ነገር በጣም ብዙ ነው።   አንድ ቀን ግን እንደሚመጣ የህይወት ተሞክሮም ሆነ የተፈጥሮ እውነታ ማርጋገጫ አልሰጠንም፤ አይሰጠንምም። በርግጥ ቀናት ይመጣሉ፤ እኛ እንደምንጠብቃቸው እርግጠኛ ባንሆንም። 

ትልቁ ትግል በምታውቀውና በተቀበልከው መንገድ ዛሬን መኖር ነው። ትልቁ ድል በምታውቀው ልክ ዛሬን መኖር ነው። መልካም ትግል።

No comments:

Post a Comment