Thursday 16 August 2012

ይህ አመት ምንድነው?


ይህ አመት ምንድነው?
በ አንጋፋዋ አርቲስት አስናቀች ወርቁ ሞት ይጀምራል፤ ይቀጥልና ሶስት የአገራችንን ሌሎች አንጋፋ ሰዎች ይነጥቀናል፤
ስብሃት ገብረ እግዚያብሄር
ማሞ ውድነህ
ሜትር አርቲስት ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ

የ አገሪቱ ፕሬዚዳንት ሞቱ ተብሎ አንዳንዶች የፌስ ቡካቸውን መልእክቶች በቁጭት አሸብርቀው፣ አንዳንዶች ሃዘናቸውን በነፍስ ይማር እየገለጹ ትንሽ ቆይቶ፣ 'የለም አልሞቱም' ተባለ፤ እፎይ የሚለው እፎይ አለ፤ ኩምትር የሚለውም ኩምትር አለ። የ ኤርትራው መሪም ኢሳያስ አፈውርቂ ሞቱ ተብሎ አለም አውርቶት፣ "አይ የለም የጠላት ወሬ ነው" ተብሎ የተስተባበለው በዚህ አመት ነበር።

ለኢትዮጵያውያን ስደተኞችም ጥሩ አመት አልነበረም። ባህር ውስጥ ገብተው አለቁ ይሉናል። http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-18531470

በዚያ አዝነን ሳንጨርስ መኪና ውስጥ ታፍነው ሞቱ ይሉናል። http://africajournalismtheworld.com/2012/06/28/dozens-of-ethiopian-and-somali-refugees-die-in-truck-in-tanzania/
ልባችንን በሃዘን የሰበርውን የሴት እህቶቻችንን የአረብ አገር እንግልት የአለም ደቻሳን ሞት ጨምሮ ማንሳት ይቻላል። አባይ ላይ የተከሰተውን አሰቃቂ የመኪና አደጋ ማስታወስም ይቻላል።

ያም ሆኖ ጉዳችን አላለቀም፤ ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም እንዲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ታመሙ ተባልን፤ አገራችን ባስተናገደችው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ መገኘት አልቻሉም፤ ታዲያ ትንሽም ሳይቆይ አንዳንዶች ሞተዋል ብለው እስከማውራት ደረሱ፤ መንግስታችን "የለም ደህና ናቸው"፤ ይህ የጠላት ወሬ ነው ብሎ ቢያረጋጋንም። እኛን ወሬ ሲፈታን የጋናው ፕረዝዳንት ግን የምር መሞታቸው ተነገረን። በዚሁ አመት የማላዊው ፕሬዝዳንት ሞት መከሰቱን ልብ ይሏል።

በቅርቡ ደግሞ ሌላ የተረጋገጠ መርዶ ደረሰን።  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ፓትርያርክ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አርፈዋል።

 http://www.danielkibret.com/2012/08/blog-post_7924.html?spref=tw

በዚሁ የኢትዮጵያውን አመት የግብጽ ኮፕቲክ ቤተክርስትያን ፓትርያርክ አቡነ ሽኖዳ መሞታቸውን ልብ ይሏል።

ዛሬ ደግሞ ለሁለት ወራት ያነጋገረን የጠቅላይ ሚኒስትራችን የጤና ሁኔታ ወሬ እልባት አገኘ። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አርፈዋል። ነፍስ ይማር!

ይህ አመት ምንድነው- ሞት የነገሰበት? የተሻለ መጭ ጊዜ ለሃገሬ እመኛለሁ።

No comments:

Post a Comment